Psalms 83

በእስራኤል ጠላቶች ላይ የቀረበ ጸሎት

የአሳፍ መዝሙር፤ ማሕሌት።

1አምላክ ሆይ፤ ዝም አትበል፤
አምላክ ሆይ፤ ጸጥ አትበል፤ ቸል አትበል።
2ጠላቶችህ እንዴት እንደ ተነሣሡ፣
ባላንጣዎችህም እንዴት ራሳቸውን ቀና ቀና እንዳደረጉ ተመልከት።
3በሕዝብህ ላይ በተንኰል አሤሩ፤
በውድ ልጆችህ ላይ በአንድነት ተመካከሩ።
4“የእስራኤል ስም ከእንግዲህ እንዳይታወስ፣
ኑና ሕዝብ እንዳይሆኑ እንደምስሳቸው” አሉ።

5በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ተማከሩ፤
በአንተም ላይ ተማማሉ፤
6የኤዶምና የእስማኤላውያን ድንኳኖች፣
የሞዓብና የአጋራውያን ድንኳኖች፣
7ጌባል፣
ቢብሎስ ለማለት ነው።
አሞንና አማሌቅ፣
ፍልስጥኤምም ከጢሮስ ሕዝብ ጋር ሆነው ዶለቱ፤
8አሦርም ከእነርሱ ጋር ተባበረ፤
የሎጥ ልጆችም ረዳት ሆነ። ሴላ

9በምድያም ላይ እንዳደረግኸው አድርግባቸው፤
በቂሶንም ወንዝ በሲሣራና በኢያቢስ ላይ ያደረስኸው ይድረስባቸው።
10እነርሱም በዐይንዶር ጠፉ፤
እንደ ምድርም ጕድፍ ሆኑ።
11መኳንንታቸውን እንደ ሔሬብና እንደ ዜብ፣
መሳፍንታቸውንም ሁሉ እንደ ዛብሄልና እንደ ስልማና አድርጋቸው፤
12እነዚህም፣ “የእግዚአብሔርን የግጦሽ ቦታ፣
ወስደን የግላችን እናድርግ” የሚሉ ናቸው።

13አምላኬ ሆይ፤ በዐውሎ ነፋስ እንደሚነዳ ትቢያ፣
በነፋስም ፊት እንዳለ ገለባ አድርጋቸው።
14እሳት ደንን እንደሚያጋይ፣
ነበልባልም ተራራን እንደሚያቃጥል፣
15እንዲሁ በሞገድህ አሳድዳቸው፤
በማዕበልህም አስደንግጣቸው።
16 እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህን ይሹ ዘንድ፣
ፊታቸውን በዕፍረት ሙላው፤
17ለዘላለም ይፈሩ፤ ይታወኩም፤
በውርደትም ይጥፉ።
18ስምህ እግዚአብሔር የሆነው አንተ ብቻ፣
በምድር ሁሉ ላይ ልዑል እንደ ሆንህ ይወቁ።
Copyright information for AmhNASV